AMHARIC NEWS

  • BBC AMHARIC
  • DW AMHARIC

በገዢው ብልፅግና ፓርቲ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ስር የሚንቀሳቀሱ እና ‘የሚዲያ ሠራዊት’ የሚል መጠሪያ ያላቸው የፓርቲው አባላት፤ መንግሥትን በሚተቹ እና በሚቃወሙ ግለሰቦች ላይ በፌስቡክ በተደረጉ የሐሰተኛ መረጃ እና በተቀናጁ ዘመቻዎች ላይ እንደተሳተፉ ቢቢሲ ያደረገው ምርመራ አረጋገጠ። [...]

በቤጂንግ የግማሽ ማራቶን የሩጫ ውድድር ቻይናዊ ሯጭን ሆን ብለው አሸናፊ አድርገውታል የተባሉት ኢትዮጵያዊ እና ኬንያዊ አትሌቶች እንዲሁም አሸናፊው ቻይናዊ ሜዳልያቸውን ተነጠቁ። [...]

የሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት ወሳኝ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እና የኤፍኤ ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎችን ያስተናግዳሉ። በኤፍኤ ዋንጫ የወቅቱ አሸናፊ ሲቲ ከ ቼልሲ ይገናኛል። የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ተፎካካሪዎቹ አርሰናል እና ሊቨርፑል ከሜዳቸው ውጪ ተጋጣሚዎቻቸውን ይገጥማሉ። የቢቢሲ የእግር ኳስ ተንታኝ ክሪስ ሱተን የጨዋታ ግምቱን እንደሚከተለው ሰጥቷል። [...]

በኢትዮጵያ ከሚገኙ የሁለተኛ እና ሶስተኛ ክፍል ተማሪች 56 በመቶዎቹ ምንም ዓይነት ቃል ማንበብ እንደማይችሉ ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ባደረገው ጥናት አመልክቷል። አገልግሎቱ በጥናቱ ተሳተፊ ካደረጋቸው የሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል ቢያንስ አንድ ቃል ማንበብ የሚችሉ 37 በመቶ የሚሆኑት ብቻ እንደሆኑ በአገልግሎቱ የትምህርት ምዘናና ምርምር መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤፋ ጉርሙ (ዶ/ር) ለቢቢሲ ገልጸዋል። የተቀሩት 63 በመቶዎቹ አንድም ቃል ማንብብ የማይችሉ (Zero renderers) ናቸው። [...]

ከአስር ዓመት በፊት በቦኮሃራም ታጣቂዎች ታግተው ከነበሩ ሴቶች መካከል አንዷ የሦስት ልጆች እናት ሆና በናይጄሪያ መንግሥት ወታደሮች ነጻ ወጣች። [...]

በትግራይና አማራ አዋሳኝ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፈታት እንዳለባቸው ምሁራን አመለከቱ። [...]

የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግሥት «ህወሓትና ግብረ አበሮቹ» ያላቸው አካላት ሁለቱ ወገኖች የይገባኛል ጥያቄ ከሚያነሱባቸውና ሰሞኑን በኃይል ከያዟቸው አካባቢዎች በአስቸኳይ እንዲወጡ አሳሰበ። የአማራ ክልላዊ መንግሥት በመግለጫው የፕሪቶሪያው ስምምነት እንዲተገበርም ጠይቋል። [...]

ከትግራይ ክልል የተነሱ ታጣቂዎች በራያ አላማጣ ወረዳ አንዳንድ ቀበሌዎች ሰሞኑን ጥቃት ማድረሳቸውን የአካባቢው ነዋሪዎችና አስተዳደሩ ተናገሩ። በግጭቱ የሰዎች ሕይወት መጥፋቱን ንብረት መውደሙንም ናዋሪዎቹና የአካባቢው ነዋሪዎች ለዶቼ ቬሌ ገልጸዋል። [...]

የጦርነቱ ጠባሳ ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ ግድም በኋላም በጉልኅ ይታያል ። ባለፉት ሳምንታት በትግራይ እና አማራ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ ታጣቂዎች መካከል ለአጭር ጊዜያት የቆዩ ግጭቶች ከአንዴም ሁለት ጊዜ መከሰታቸው ነዋሪዎችን እጅግ አስግቷል ። [...]

የአማራና የትግራይ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ግጭት መከሰቱ ለምን? ጠ/ሚ አቢይ አሕመድ ከመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞች ጋር እንዲወያዩ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት መጠየቁ፤ በኢትዮጵያ ለሚታየዉው የከፋ የሰብዓዊ ቀውስ ምላሽ ለመስጠት በመንግሥትና ዓለምአቀፍ አጋሮች በተጠራው የገንዘብ ማሰባሰብ 610 ሚሊዮን ዶላር መሰብሰቡ። [...]

ዜና