AMHARIC NEWS

  • BBC AMHARIC
  • DW AMHARIC

ሰኞ ሚያዝያ 14/2016 ዓ.ም. የመን ውስጥ በስደት ሲንከራተቱ ቆይተው ወደ አገራቸው ለመመለስ የተነሱ ሰባ ሰባት ኢትዮጵያውያንን አሳፍራ ወደ ጂቡቲ ያቀናችው ጀልባ ወደ ባሕር ዳርቻው ብትቃረብም በሰላም ካሰበችበት አልደረሰችም። በገጠማት የመገልበጥ አደጋ ከ20 በላይ ኢትዮጵያውያን ባሕር ላይ ቀርተዋል። ከአደጋው የተረፈ አንድ ኢትዮጵያዊ አደጋው እንዴት እንደተከሰተ ለቢቢሲ ተናግሯል። [...]

አህጉረ አፍሪካን በፍጥነት በሩጫ በማቋረጥ ክብረ-ወሰን ለመስበር ያለመው ግለሰብ በደኅንነት ስጋት ምክንያት ዕቅዱ ሊከስምበት እንደሆነ ተናግሯል። [...]

በዕድሉ መንገሻ እና አበባ ተስፋዬ በተለያየ ጊዜ ከሱዳን ተነስተው፣ የሊቢያ በርሃን አቆራርጠው፣ የሜድትራኒያንን ባህር ሰንጥቀው ነበር ጣልያን የደረሱት። በዚያ ጉዞ የሰው ልጅ ሊሸከመው የማይችለው ፈተናን አይተዋል። ጭው ባለ በርሃ የሰው ልጆችን የሰውነት ቅሪት እየተመለከቱ፣ እየተደበደቡ፣ እየተራቡ፣ እየተጠሙ እና በህይወታቸው ‘እየቆመሩ’ የተመኟትን ጣልያን ከረገጡ ዓመታትን አስቆጥረዋል። ተስፋ ያደረጓት ጣልያን እንዴት ተቀበለቻቸው? ጣልያን ለኢትዮጵያን ስደተኞች ምን ያህል ምቹ ናት? የቢቢሲ ጋዜጠኞች ጣልያን በሄዱበት ወቅት ታሪካቸውን አጋርተዋል። [...]

ሐሰተኛ ሰነድ በመጠቀም ከስድስት ሚሊዮን ዶላር በላይ ለማውጣት በመሞከር የተጠረጠሩት ቀሲስ በላይ መኮንን፤ ድርጊቱ በተፈጸመበት ቦታ የተገኙት “ሰዎች አታልለዋቸው” እንደሆነ ለፍርድ ቤት መግለጻቸውን ጠበቃቸው አቶ ቱሊ ባይሳ ለቢቢሲ ተናገሩ። [...]

በኬንያ መዲና ናይሮቢ በተከሰተ ከባድ ጎርፍ መንገዶች በውሃ ተጥለቅልቀው የታዩ ሲሆን የሀገሪቱ ባለስልጣን የጎርፉ መጠን “እጅግ በከፋ ደረጃ እየጨመረ ነው” ብለዋል። [...]

በአማራና ትግራይ የይገባኛል ጥያቄ በሚነሳባቸው አካባቢዎች በተከሰተ ግጭት ከ50 ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ያለፈው ሰኞ አስታውቋል። እንደ ድርጅቱ በሺህዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች አስቸኳይ የሰብዓዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን፤ በተለይ ሴቶችና ህጻናት የሚገኙበት ሁኔታም አሳሳቢ ነው። [...]

በትግራይና አማራ አዋሳኝ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፈታት እንዳለባቸው ምሁራን አመለከቱ። [...]

“ከትግራይ ክልል ተሻግረው የመጡ” ያሏቸው ታጣቂዎች ጥቃት እንዳደረሱባቸው የራያ አላማጣ ወረዳ ባለስልጣናትና ነዋሪዎች ለዶይቼ ቬሌ ተናገሩ። ጉዳዩን አስመልክቶን ከትግራይ ክልል የመንግስት የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃአስተያየት ለማካተት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡ የፕሪቶሪያው ስምምነት በህገመንግስቱ መሰረት እንደሚፈታ ዉሉ ያትታል፡፡ [...]

ከአላማጣ ከተማ ተፈናቅለው በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ ጃራ የመጠለያ ጣቢያ ከአንድ ዓመት በላይ ይኖሩ የነበሩ የአላማጣ ከተማ ተፈናቃዮች በመንግስት ድጋፍ ትናንት ወደ ቀያቸው መመለሳቸውን የአካባቢው አስተዳደርና ተፈናቃዮች ተናገሩ፣ በመጠለያ ጣቢያው ከአላማጣ፣ ባላ፣ ኮረምና ኦፍላ የተፈናቀሉ ከ 30 ሺህ በላይ ሰዎች ይኖሩበት ነበር ተብሏል፡፡ [...]

ከብልፅግና ጋር የሚያገናኘው የጋራ አጀንዳው የፕሪቶርያው ውል መሆኑን የገለጸው ህወሓት ውሉ በሙሉ እንዲተገበር አጋዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ብልፅግና ፓርቲና ህወሓት በመቐለና አዲስአበባ መወያየታቸውን አስታውቋል። ከዚህ ውጭ ህወሓትና ብልፅግና ፓርቲ በመገናኛ ብዙሐን እንደተባለው የጀመሩት ወደ ውህደት የሚመራ ውይይት የለም ሲል አስተባብሏል። [...]

ዜና